TVET Logo
Home | Statistics | Publications | TVET Institutions| Comments | Contacts
 
 

Content on this page requires a newer version of Adobe Flash Player.

Get Adobe Flash player

   

Lapidary...

የተፈጥሮ ሀብታችን በአግባቡ በመጠቀም ከድህነት ለመውጣት የሚደረገውን ጥረት ለማሳካት በክልላችን የሚገኘውን የከበረ ድንጋይ በአግባቡ ለመጠቀም ከስልጠናውም በሚገኝ ክህሎት የከበሩ ድንጋዮችን በመቁረጥና በማስዋብ የአገር ውስጥና የውጭ አገር ገበያ በመፍጠር የክልሉን የኢኮኖሚ አቅምና ገጽታ ለመለወጥ ያስችል ዘንድ የከበረ ድንጋይ ልማትን ለማስፋፋት የተቀናጀ ፕሮግራምና ዕቅድ አዘጋጅቶ ተግባራዊ የማድረግ ኃላፊነት የተሰጠው የፕሮጀክት ጽ/ቤት በክልሉ መስተዳድር ምክር ቤት ደንብ ቁጥር 54/1999 ተቋቁሞ በርካታ ተግባራትን አከናውኗል፡፡ 

የክልሉን ተጠቃሚነት የበለጠ ለማረጋገጥና በፕሮጀክት ጽ/ቤቱ ስር በተቋቋሙ 17 የስልጠና ማዕከላት ሰልጣኞችን በመመልመል ወደየ ስልጠና ማዕከላት ከማስገባት ጀምሮ ስልጠናውን ያጠናቀቁ ሰልጣኞች ወደ ስራ እስከ ማሰማራትና በስራ ስምሪትም ክትትልና ድጋፍ እስከ ማድረግ የሚዘልቅ ተግባራትን መፈፀም የሚያስችል በውድድር ላይ የተመሰረተ፣ ቀልጣፋና ጥራት ያለው፣ ክልሉን በከበረ ድንጋይ ሃብት ልማት ቀዳሚ ማድረግ የሚችል አዲስ የስራ ሂደት በመቅረጽ ወደ ትግበራ ለመግባት በዝግጅት ላይ እንገኛለን፡፡

   

 

     
 
 
 
 
Related Links for this Page...
 
   
 

 Copyright 2011 ANRS Technical Vocational Bureau. Designed by Adewale Adeniyi-Kie